#50ኛ_አመት_እዩቤልዩ_ጉባኤ
#በሀዋሳ_01_እናት_አጥቢያ_የምረቃ_ፕሮግራም
#Apostolic_Church_Of_Hawasa
#Apostolic_Church
የአዋሳ አጥቢያ ቤተክርስቲያን!
በ1965 ዓ.ም!
📌የአዋሳ ምዕመናንና ተክለማርያም (ቢ/ፕ) "በአዋሳ የማምለክያ ቦታ ከመንግስት ማስፈቀድ አለብን" በሚል አርዕስት ጸሎት ጀመሩ። በጊዜው የአገሪቱ ፖሊሲ ሶሻሊዝም ስለነበረ የሐይማኖት ነገር ቦታ አልነበረውም።
📌 አንድ ቀን ተክለማርያም ቦታ ለመጠየቅ የክፍለሀገሩ ም/ዋና አስተዳዳሪ የሚመሩት የትርፍ ቤትና የትርፍ ቦታ ኮሚቴ ውስጥ በቀለ ፈዬ (ቢ/ፕ) ተመድቦ ስለሚሰራ "ማመልከቻ ጽፈን በእርሱ በኩል እንዲጠየቅ ብናደርግ ጥሩ ነው" ብሎ ሃሳብ አቀረበ። የተጻፈውን ማመልከቻ በቀለ ለም/ዋና አስተዳዳሪው አቀረበና እንዲሰጣቸው የሚል ትዕዛዝ ለከተማ ልማት አስመራ።
📌 አሁን የአዋሳ ቤተክርስቲያን የተሰራበት አከባቢ ቦታ እንድጠቁሙ አጥብቀው ሲጸልዩ እግዚአብሔር በራዕይ ለአንዲት እህት አሳየ። ከዚያ ቦኃላ በራዕዩ መሠረት የተጠቆመው ቦታ "መንግስት ለመዋለ ሕጻናት ያቀደው ማዕከል ስለሆነ አይሆንም፤ ነገር ግን ከፈለጋችሁ ከከተማ ውጭ ማለትም ከታቦር ተራራ ጀርባ ይሰጣችሁ" ባለስልጣናት መለሱ። እነርሱም "ሰው ለጽድቅ ብሎ ኢየሩሳሌም ድረስ ይሄዳል፤ እኛም ለዚህ እውነት እዚያ ድረስ ብንሄድ ምንም አይደለምና ብቻ የትም ይሁን መሬቱ ይሰጠን" አሉ። በዚህ ሁኔታ መሬቱ ሊሰጥ ተወሰነ።
📌 ነገር ግን መጀመሪያ ስለታየው ራዕይ ከኢየሱስ ጋር ትልቅ ክርክር ነበር። ምክንያቱም "በመንፈስ የታየው ነገር እንዴት ሳይሳካ ቀርቶ ከከተማ ውጭ እንወረወራለን" እያሉ በጸሎት ላይ እያሉ ቀኑ ደረሰና ያን ቦታ ልረከቡ መሃንዲሱ ለክቶ ልሰጣቸው ሲሄዱ በመሬቱ ላይ እዛው አከባቢ ያሉ የአከባቢው ሰዎች በቆሎ ዘርተውበት ስለነበር " በቆሎው ተነስቶ ነው የሚሰጣችሁ" ተብሎ ሳይሳካ ቀረ። ይህም የኢየሱስ አላማ ነበር።
📌 ነገሩ በዚህ ተቀየረና በቆሎ ተነስቶ እንደገና መሬቱን መሃንዲስ እንዲለካና እንዲሰጥ፤ ተክለማርያምም ከአዲስ አበባ ተጠርቶ ወደ አዋሳ መጣ። ቀጥሎ ከመሃንድሱ ጋር ወደ ቦታው ሲሄዱ በቆሎው ተነስቷል፤ ነገር ግን ሁኔታው ተቀየረ። እግዚአብሔር ቀየረውና የእግዚአብሔር መንፈስ ቄስ ኃይሉ ፈንታውን አንድ ነገር አናገራቸው፤ ንግግሩም እንዲህ የሚል ነበር "ምድርና መላው አለም የእግዚአብሔር ነው፣ ነገር ግን እግዚአብሔር ቤተክርስቲያኑን ለማሳረፍ በዚህ ምድረበዳ መወርወሩ ይገርማል" የሚል ነበር።
📌 በዚህ ጊዜ መሃንዲሱ ደንግጦ "አቶ ኃይሉ ለምን ሃይለኛ ንግግር ይናገራሉ?" አለ። "ልክ አይደለም እንዴ?" አሉ ቄስ ኃይሉ። መሃንዲሱም በዚህ ንግግር ደንግጦ "ያኔ የጠየቃችሁ ቦታ አለ! ማዕከል መሆኑ ቀርቷል፤ እሱን ልስጣችሁ?" አለ። "የእኛ ጥያቄማ እሱ ነበር" ብለው መለሱለት። በዚህ ጊዜ መሃንድሱ የዘረጋውን ሜትር እንደገና ጠቅልሎ "በቃ ወደዚያ እንሂድ እሱ ይሰጣችሁ" አለ። እግዚአብሔር በመንፈስ የተናገረው እውነት ሆነ፤ መሬቱም ተለክቶ ተሰጠ።
📌 የእግዚአብሔር ቤተከርስቲያን አሁን ባለችበት ቦታ ተጀመረች። ምንም ገንዘብ አልነበረም፤ ነገር ግን እጅግ የሚቀኑ ክርስቲያኖች ነበሩ፤ በጉልበታቸው የሚሰሩ ወንድሞችና እህቶች ተነሱ። ጌታ ኢየሱስ ተክለማርያምን አዋሳ ሂድ ያለው አዋሳን የወንጌል ስርጭት መነሻ ለማድረግ አስቦ እንደነበር ከፍሬው መረዳት ይቻላል።
📌 የሐዋርያት ቤተክርስቲያን አሁን የደረሰችበት ዕድገት በቀላል ጉዞ የደረሰች አይደለም። ብዙ ችግሮችንና መከራዎችን አሳልፋለች። አገልጋዮቿ በመገረፍ፣ በርሃብ፣ በራቁትነት፣ የመኖሪያ ቤት ኪራይ በማጣትና በመንከራተት፣ በመታሰር፣ ልጃቸውን በስደት በሞት በማጣት በዚህ ሁሉ ይሰቃዩ ነበር። ይሁን እንጂ በዚህ ሁሉ ስለ ወንጌል ከመናገርና ከመመስከር በየገበያ ሳይቀር ከመስበክ በስተቀር በስደት ፍርሃት ወደ ኃላ ያለ የለም።
📌 በስደት ምክንያት አይናቸውን ያጡ ምዕመናን ነበሩ። ነፍሳቸውን በሞት የተነጠቁም ነበሩ። በዚህ ሁሉ የወንጌል ስርጭትና የነፍስ ማዳኑ ፍጥነት እየተቀጣጠለ ሄደ እንጂ ሊቆም አልቻለም። ኢየሱስ ከቤተክርስቲያን ጋር ብዙ ተአምራቶችን ሠርቶአል። በቃሉም እንዲጸኑ አድርጓል። ከተናገረውም ሁሉ ሲዳማን ሁለተኛ ኢየሩሳሌም አደርጋታለሁ ብሎ ነበር፣ አደረገ! የዋራ ቤቴል ምስክር ነው። ከአለም ዙሪያ ሁሉ ወደ ዋራ ቤቴል ጉባኤ ለበረከት የማይመጣ የለም። ክብር ለኢየሱስ ይሁን! እግዚአብሔር አይዋሽም! በራዕይም፣ በድምጽም፣ በትንቢትም፣ በቃልም ይናገራል።
📌 የኢትዮጵያ ሐዋሪያዊት ቤተከርስቲያን እምነት ተረካቢ ትውልድ መሠረቷን ሳይለቅ በመሠረቷ ላይ እየገነባ እንዲያንጽና እንዲያሳድግ በንጹሕ አዕምሮ፣ በሚሰማውና በሚያየው በአለም ነገር ሳይቆሽሽ፣ አይንና ጆሮውን ወደ አምላኩና ወደ እግዚአብሔር ቃል አድርጎ ወደፊት ወንጌሉን ማስቀጠል እንዳለበት መገንዘብ ይገባዋል። ከመጀመሪያው ስደት ይልቅ የዚህ ትውልድ ስደት ይጠነክራል! እናስተውለው!
Stay blessed!
• 50ኛ አመት ኢዮቤልዩ ጉባኤ | በሀ...
Негізгі бет 50ኛ አመት ኢዮቤልዩ ጉባኤ | በሀዋሳ 01 እናት አጥቢያ የምረቃ ፕሮግራም | Apostolic Church Of Hawasa | Apostolic Church
Пікірлер: 29