ይህን ገጠመኝ ስትሰሙ እንደምእመን ስሙ
እኔ ደግሞ እንደአገልጋይና እንደምእመን የሁሉንም ወቀሳ ተሸክሜ ይኸው የተወቀስንበትን መልእክት አቅርቤአለሁ
በነገራችን ላይ የባለታሪካችንን ነፍስ ይማርልንና እን ይህን ገጨመኝ ሳዳምጠውና ስፅፈው ዘመኔን ወደ ቀደሙት አባቶችና እናቶች ወስጄ ነው ያዳመጥኩትና የተቀበልኩት
እንደዚህኛው ትውልድ ማንነትና ልቦና ባዳምጠው ኖሮ ብዙ ጥያቄ ኖሮኝ ደርሶ ፈራጅ ነበር የምሆነው
ስለዚህ ቤተሰቦቼ እን የገድላትና የስንክሳር ታሪኮችን ብቻ ሳይሆን የዘመኔንም ትሁቶች እቀበላለሁ
ይህ ማለት ግን ሳያመዛዝን በጭፍን ቲፎዞ የሆነውን ምእመንንም እወቅሳለሁ ማለቴም ጭምር ነው
በተለይ አገልጋይና ሰባኪ ሆነን ሳለ ግን ሳናረጋግጥና ያለእምነት መነፅር እንዲሁ ለታይታ የምንሰነዝረውን የተቃውሞ ሀሳብም እነቅፋለሁ
የአባታችንን እድሜ ያርዝምልን የምንለው በምክንያት ነው
እሳቸው ከየትኛውም ማህበርና የግል አስተሳሰብ ነፃ የሆኑ ምርጥ አባት ናቸው ወደዛና ወደዚህ ማለት የማይወዱ ዝምተኛ ሰባኪ ናቸው ፀጋቸውን ላለማስነጠቅ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ወደብቃት እየወሰዳቸው እንደሆነ በቅርብ ርቀት አይቻለሁ
አንዳንዶች የተቀበሉትን ፀጋ ያስነጠቁት ስለማያውቁት ነገር በመዘባረቅ ነው
የእውነት መልዕክት መጥቶላቸው ግን የራሳቸውን ፍልስፍና ሲቀላቅሉ ፀጋቸውን የተነጠቁም አሉ
Негізгі бет 65ኛb ገጠመኝእመቤታችን እኔን ገሰፀችኝ ( በመምህር ተስፋዬ አበራ )
Пікірлер: 516