ዓድዋ በህብር የጸናች ሀገርን ለመፍጠር መሠረት የጣለና አሁንም የትውልዱ አሻራ ሆኖ የታላቋን ሀገር ትልቅ ስዕል የሚያሳይ የታሪካችን ዋነኛ ምዕራፍ ነው፡፡ ዓድዋ የማይደፈረውን የቅኝ ገዥዎችን የበላይነትና ፍላጎት መና ያደረገ፣ የታሪክ አንጓ ነው። ዓድዋ የጥቁር ሕዝቦች ኩራት፣ የአፍሪካዊያን የትግል አርማና የመንፈስ ጥንካሬ ምንጭ በመሆኑ አስተሳሳሪ ቅርሳችን ነው፡፡
ዓድዋ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ በሀገር ፍቅር ገመድ ያሰናሰነ፣ የሀገር ሉዓላዊነትን ከአካባቢያዊ ልዩነት ያስቀደመ የነፃነት ብስራት ሲሆን፤ ለጠላቶቻችን ደግሞ ሀፍረትን ያከናነበ የኢትዮጵያ ህብረብሔራዊ አንድነት የጸናበት የማእዘን ድንጋይ ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ በመሐል ፒያሳ የተገነባው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ፕሮጀክትም የዚሁ የወል እዉነት ዋና አካል መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል። ፕሮጀክቱ የዓድዋ ድልን በሚመጥን ደረጃ ተገንብቶ ለእይታ መብቃቱ የጋራ ድሎችንን በማጉላት፣ ከፋፋይ ትርክቶችን በዘላቂነት በማክሰም የወል ትርክቶች እንዲገነቡና ወደ ትውልድ እንዲተላለፉ በማድረግ የኢትዮጵያን ህብረ ብሔራዊ አንድነትና ወንድማማችነት ስር እንዲሰድ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡
የዓድዋ ድል ለኢትዮጵያዊያን ብቻም ሳይሆን ለጥቁር ሕዝቦች የትግል አርማና የመንፈስ ጥንካሬ ምንጭ ነበር፡፡ የዓድዋ ድል መታሰቢያ የአፍሪካ መዲና በሆነችዉ አዲስ አበባ እምብርት መገንባቱ ለኢትዮጵያውያን መታሰቢያነት ብቻም ሳይሆን ለነፃነታቸው ለታዋደቁ አፍሪካያን ወንድሞችም ጭምር መሆኑን ያሳያል፡፡
Негізгі бет Ойын-сауық ዓድዋ በልኩ ሲዘከር Honoring Adwa in full glory አድዋ ሙዜም ገፅታ
Пікірлер