አትሮኑስ፡፡
ጤና ይስጥልን ውዶቻችን፣ እነሆ አትሮኑስ፡፡ መቼም የአትሮኑስ ዝግጅታችን ህይወትን፣ ርእዮትንና መጻህፍትን የምንገልጥበት እንዲሁም ታሪክን የምንፈትሽበት መሆኑን ታውቃላችሁ፡፡ ዛሬ እንድታነብቡት የምንሻውን መጽሀፍ በጥቂቱ ልናቃምሳችሁ ፈልገናል፡፡ ይህንን የመጽሀፍ ጠዲቅ ከተቃመሳችሁ በኋላ ይህንን መጽሀፍ አትሮኑሳችሁ ላይ አኑራችሁ እንደምትገላልጡት፣ እንደምትኮመኩሙት ተስፋችን የጸና ነው፡፡
ዛሬ በአትሮኑሳችን የምንገልጠው ፊታውራሪ ተክለሀዋርያት ተክለማርያም AUTO bioGRAPHY የህይወቴ ታሪክ የተሰኘውን መጽሀፍ ነው፡፡
መጽሀፉን ከመግለጣችን በፊት ግን ስለተክለሀዋርያት ተክለማርያም ጥቂት እናውጋችሁ፡፡ ተክለሀዋርያት ተክለማርያም በ20ኛው ክፍለዘመን አጥቢያ ወደውጪ ተልከው ከተማሩ ታላላቅ ምሁራንና ፖለቲከኞች አንዱ ናቸው፡፡ በ1923 ስራ ላይ የዋለውን የኢትዮጲያን የመጀመሪያ ህገመንግስት በማርቀቅ ከፍ ያለ ሚና ተጫውተዋል፡፡ ፊታውራሪ ተክለሀዋርያት በሸዋ የተወለዱ ሲሆን፣ በቤተክህነት ትምህርት ካለፉ በኋላ በ9 አመታቸው ራስ መኮንን ገዢ ወደነበሩበት ወደሀረር ከተማ ሄዱ፡፡ ተክለሀዋርያት የእርሳቸው የቅርብ ዘመድና የተፈሪ መኮንን (ኋላ ንጉሰነገስት ቀዳማዊ ሀይለስላሴ) አባት ከሆኑት ከራስ መኮንን ጋር ጣልያንን ለመዋጋት አብረው ዘምተዋል፡፡
ራስ መኮንንም የሩስያ የቀይ መስቀል ማህበር አባል ከነበረው ከመስፍን ኒኮላይ ሊዮንቲፍ ጋር ስላገናኟቸው ሩስያ ሄደው ለመማር እድል አገኙ፡፡ እንደአውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1901 ወደሩስያ ተጉዘውም በቅዱስ ፒተርስበርግ አካዳሚ ገብተው፣ የመድፈኝነት ትምህርት ተከታትለው የኮለኔልነት መአርግ አብኝተዋል፡፡ በሩስያም 17 አመታት ቆይተዋል፡፡
ወደኢትዮጲያ ተመልሰውም በመንግስት አስተዳደር ዘዬአቸው፣ በፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎቻቸው፣ ህገመንግስት በማርቀቅ ሚናቸው እንዲሁም በጻፏቸው ቲያ,ትሮች እውቅ ምሁር ነበሩ፡፡ የንግስተነገስታት ዘውዲቱ ደጋፊ የነበሩ ቢሆንም፣ በወቅቱ የነበረውን አስተዳደር ሙሰኝነትና የሀገሪቱን ፍርድ ቤቶች ኋኋላ ቀርነት እያነሳ የሚተች ፋቡላ የተሰኘ ቲያትር በመመድረካቸው፣ ንግስት ዘውዲቱ ቲያትሮች በአጠቃላይ በሀገሪቱ እንዳይቀርቡ አገዱ፡፡ ዘመናዊ ቲያትርን ለአገራችን ተመልካች በማስተዋወቅም ከቀዳሚዎቹ መሀል ናቸው፡፡ ቲያትሩ ተምሳሌታዊ፣ እንስሳት በገጸባህሪነት የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የሚወክሉበትና በፍርድ ቤቶች ላይ ጠንከር ያለ ሂስ የሚሰነዝር ነበር፡፡
ፊታውራሪ ተክለሀዋርያት በህይወታቸው ያዩ የሰሙትን፣ ያነበቡ የሰሙትን፣ ያስተዋሉ የተረዱትን AUTOBIOGRAPHY የህይወቴ ታሪክ በሚል ርእስ ውብ መጽሀፍ ሰጥተውን አልፈዋል፡፡ ስለዚህም በኢትዮጲያ እጅግ ወሳኝ በሆኑ ታሪካዊ ፍጻሜዎችና ሂደቶች ላይ በአካል የተካፈሉና የአይን እማኝም በመሆናቸው፣ ዛሬ በአትሮኑሳችን ይህንን መጽሀፍ ገልጠናል፡፡ ይህንን የመጽሀፉን ክፈፍል አብራችሁን ከተቃመሳችሁ በኋላ መጽኀፉን ፈልጋችኁ እንድታጣጥሙ ጋብዘናችኋል፡፡
ፊታውራሪ ተክለሀዋርያት ተክለማርያም AUTO bioGRAPHY ወይም የህይወቴ ታሪክ ወደተባለው መጽሀፍ ገጽ 267 ሄድን፡፡ አብራችሁን ሁኑ፡፡ አትሮኑስን አድምጡ፡፡ ሀሳቦቻችሁን በአስተያየት መስጫ ስፍራው ላይ አኑሩልን፡፡ ላይክና ሼር ማድረግ አትዘንጉብን፡፡ ሰብስክራይብም አድርጉና የርእዮትም የአትሮኑስም ቤተሰብ ሁኑ፡፡
Негізгі бет Ойын-сауық Atronos: Council and Power // አትሮኑስ፣ ምክርና ስልጣን፣ ተክለሀዋርያትና ልጅ እያሱ
Пікірлер: 2