እነሆ ከዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ጋር ካካሄድነው ተከታታይ ጭውውት ተከታዩን ክፍል አድምጡ፡፡ ዳኛቸው በ1964 አ.ም እንደኢትዮጲያ አቆጣጠር ከሀገሩ ከመውጣቱ አስቀድሞ በተማሪዎች እንቅስቃሴ ጊዜ እና ሁኔታው በፈቀደለት ልክ የተካፈለ፣ ኋላም ለ30
አመታት በዩናይትድ እስቴትስ በኖረበት ጊዜ መጀመሪያ ከኖርዝኢስተርን ዩኒቨርሲቲ በፖለቲካል ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪውን፣ ለጥቆም ከቦስተን ካቶሊክ ኮሌጅ በፍልስፍና ሁለተኛ እና ሶስተኛ ዲግሪውን ያገኘ ኢትዮጲያዊ ምሁር ነው፡፡ዶክተር ዳኛቸው
ከረዥም የስደት ዘመን በኋላ ወደሀገሩ ተመልሶ ለአመታት በአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና ትምህርት ክፍል በመምህርነት ቢያገለግልም፣ አቋሞቹን በግልጽ በልዩ ልዩ መንገድ በመግለጹያለአግባብ እና ፍትህ በጎደለው ሁኔታ የምርምር እና የቀደሙ ሀሳቦች
ማእከል ሊሆን ይገባው ከነበረው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተሰናብቷል፡፡ ሆኖም ዳኛቸው አሁንም የአደባባይ ምሁር ሊወጣ የሚገባውን ድርሻ ማበርከቱን ቀጥሏል፡፡
Негізгі бет Atronos with Dr. Dagnachew Asefa: Part 2 of 5
Пікірлер: 21