welcome to" መክሊት ዘተዋሕዶ " KZitem channel This channel is the official channel of Meklit the Tewahido" መክሊት ዘተዋሕዶ " you will find ancient Ethiopian church history, preachings ,and other videos.
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸----🔸🔸🔸🔸🔸
ታህሳስ 23
፨ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
🔸 ቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ ይላል:- "እግዚአብሔር ለዳዊት በእውነት ማለ: አይጸጸትም::" (መዝ. 131:11) አሁን በእግዚአብሔር መጸጸት ኑሮበት አይደለም:: ቅዱስ ዳዊት የማያጸጽት ፍጹም ወዳጅ መሆኑን ሲገልጥ ነው እንጂ:: ጌታ ቅዱስ ዳዊትን "እንደ ልቤ የሆነ: ፈቃዴን የሚፈጽም: ባሪያየን ዳዊትን አገኘሁት" (መዝ. 88:20)
እንደ አምላክ ልብ ሆኖ መገኘት ምን ይረቅ?! ምንስ ይደንቅ? ለዚህ አንክሮ ይገባል።
ቅዱስዳዊት አባቱ እሴይ እናቱ ሁብሊ ይባላሉ። በነሐሴ 13 ቀን ተጸነሰ በሚያዝያ 6 ቀን በይሁዳ በቤተልሔም ሀገር ተወለደ። (1ሳሙ. 16፡10-11) ዳዊት ማለት ልበ አምላክ ማለት ነው። እረኛና ብላቴና ነበር።
· የፍልስጤማውያኑን ሰው ጎልያድን በ12 ዓመቱ 5 ጠጠርን ከወንዝ ለቅሞ በወንጭፍ ወርውሮ የገደለ (1ሳሙ.12፡45-51)፣ ንጉሥ ሳዖል በጌልቦአ ተራራ በራሱ እጅ ከሞተ በኋላ አስቀድሞ በይሁዳ 7 ዓመት በመላው እስራኤል 33 ዓመት የነገሠ (2ሳሙ. 2፡4፤ 2ሳሙ. 5፡1-5) ቅዱስ አባት ነው።
· “እግዚአብሔር እንደ ልቡ የሆነ ሰው መርጦአል” (1ሳሙ.13፡14) ተብሎ በእግዚአብሔር የተመረጠና ነገረ ሥጋዌን፣ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን፣ ዳግም ምጽዓትን፣ ነገረ ማርያምን፣ ክብረ ቅዱሳንን፣ በስፋትና በጥልቀት የተናገረ የብሉይ ኪዳን “ወንጌላዊ” ነበር። (መዝ.21 (22)፡ 16-18 “ብዙ ውሾች ከብበውኛልና የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ። አጥንቶቼ ሁሉ ተቈጠሩ እነርሱም አዩኝ ተመለከቱኝም። ልብሶቼን ለራሳቸው ተከፋፈሉ፥ በቀሚሴም ላይ ዕጣ ተጣጣሉ።…”፣ መዝ. 46(47)፡4-5 “አምላክ በእልልታ፥ እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።”፣ መዝ.49(50)፡ 1-5 “ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊት ይቃጠላል፥ በዙሪያውም ብዙ ዐውሎ አለ።”፣ መዝ. 44(45)፡9 “የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች።”
· ዳዊት ታላቅና ገናና ንጉሥ ከመሆኑ የተነሳ መንግሥቱ የመሲህ መንግሥት ምሳሌ ሆኗል፤ መሲሁም ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዳዊት ስም ብዙ ጊዜ በመጽሐፍቅዱስ ተጠቅሶ ይገኛል። (ት.ኢሳ.9፡7፣ ኤር.23፡5-6፣ ኤር.3314-17፣ ህዝ. 34፡23፣ሆሴዕ 3፡5)
· ቅዱስ ዳዊት 7 ሀብታት የተሰጡት አባት ነበር፤ እነዚህም ሀብተ ክህነት፨ ሀብተ መንግሥት፨ሀብተ መዊዕ፨
ሀብተ ትንቢት፨ሀብተ ኀይል፨ሀብተ በገና፨ሀብተ ፈውስ፨ ናቸው።
· እድሜ ዘመኑን እግዚአብሔርን በማገልገልና በመፍራት ኖሮ በታህሳስ 23 ቀን አርፎ በኢየሩሳሌም ተቀብሯል። በረከቱ ይደርብን
የመክሊት ዘተዋሕዶ ቤተሰብ ይሁኑ።
Негізгі бет ነብየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት መክሊት ዘተዋሕዶ
Пікірлер: 33