ግጥም
+++
አድነኝ አምላኬ አድነኝ
+++++
መዝሙረ ዳዊት Psalms11(12)
አድነኝ አምላኬ አድነኝ
አድነኝ ጌታዬ አድነኝ
አልቋል ከምድር ላይ ደግ ሰው
እንባዬን ከአይኔ ላይ አብሰው/2
ፍቅር ከሰው ልጆች ቀዝቅዞ
ትዉልዱ በበደል ተይዞ
ወዳጅ በወዳጁ ጨከነ
ወዉደዱ የሽንገላ ሆነ/2
ሆኖበት ክብሩ በነውሩ
ተጣሰ የፍቅር ድንበሩ
ደርቦ የማይሞቀዉ ሆነ
ደስታዉ ከእጁ ላይ ተነነ/2
ለቃልህ መታዘዝ ዘነጋ
ተክዞ መሽቶ እየነጋ
ለክፉ አሳልፎ ሰጠ
ወንድሙን በነዋይ ለወጠ/2
ትንኝን ያጠራል ከሰው ላይ
በራሱ ምሶሶዉን ሳያያይ
ይሆናል የወንድሙ ፈራጅ
ተይዞ በእግዚአብሄር እጅ/2
ተሰዶ ሲኖር በባእድ
ሲገባው ሁሉም ሊዋደድ
አንዱበአንዱ ላይ ይነሳል
አካሉን ቀኝ እጁን ይንቃል
ወንድሙን እህቱን ይንቃል
++++
መዝሙረ ዳዊት 121:1 አቤቱ፥ አድነኝ፤ ደግ ሰው አልቆአልና፥ ከሰው ልጆችም መተማመን ጐድሎአልና።
Негізгі бет አድነኝ አምላኬ አድነኝ ዘማሪት ሲ/ር ፋሲካ መኮንን
Пікірлер: 111