የመሰንቆው ሊቅ»፤ ጌታመሳይ አበበ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአሥር በላይ በሚሆኑ ትያትሮች ላይ ተዉነዋል። የአቤ ጉበኛ «የደካሞች ወጥመድ» ፣ የብርሃኑ ዘሪሁን «የለውጥ አርበኞች» እና የጌታቸው አብዲ «ስንት አየሁ» ትያትሮች ተጠቃሽ ናቸዉ። ከ38 ዓመታት በላይ በሀገር ፍቅር ትያትር በአገለገሉበት ዘመን ጌታመሳይን በቅርበት በቅርበት ለማወቅ እድሉ እንደነበራቸዉ የነገሩንና በአሁኑ ወቅት የዮድ አቢሲኒያ ሙዚቀኞች መሪ አቶ አዱኛ ቸኮል፤ ጌታመሳይ ሁለገብ ከያኒ መሆናቸዉን በሰፊዉ አጫዉተዉናል።
በመሰንቆ፤ ሰሜን አሜሪካ፣ አውሮጳና አፍሪቃ በመዟዟር የኢትዮጵያን የባሕል ሙዚቃ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያስተዋወቁ አንጋፋ ድምፃዊ፤ የሙዚቃ መሣርያ ተጫዋችና ተዋኝ ነበሩ።
ሚያዚያ 8 ቀን 2008ዓ.ም በ 72 ዓመታቸዉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ሚያዝያ 9 ቀን በመንበረ ጸባኦት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈፀመ። የዝግጅት ክፍላችን ለቤተሰብ ዘመድ ወዳጅ ጓደኛ ሁሉ መፅናናትን ይመኛል። ነፍስ ይማር!
«የሽምብራው ጥርጥር የዛፎቹ ፍሬ የትም የትም ዞሬ ትዝ አለኝ ሀገሬ» «የመሰንቆው ሊቅ» ጌታመሳይ አበበ ዘመን ተሻጋሪ ከሆኑ የባህል ሙዚቃ ጨዋታዎች በግንባር ቀደምትነቱ የሚታወቀዉ ነዉ።
Негізгі бет Ethiopia best music lyrics ጌታ መሳይ አበበ የሽንብራዉ ጥርጥር
Пікірлер: 17