ጎሥዓ ልብየ ቃለ ሠናየ /፪/
ወአነ አይድእ ቅዳሴሃ ለማርያም /፬/
እኔስ የማርያምን ውዳሴዋን እናገራለሁ
እንደ አባቴ ዳዊት በበገና እዘምራለሁ
ቀን ከሌሊት ሳልል ለምስጋና እተጋለሁ
ምርኩዜ ነሽና እመቤቴ በአንቺ እመካለሁ
ኦ እመቤቴ በእውነት እንወድሻለን
የእውነተኛ መብልን ክርስቶስን ወለድሽልን
ምክንያተ ድኂን ሆይ ድንግል ማርያም የአምላክ መገኛ
በአማላጅነትሽ በመታመን እንጮሃለን እኛ
ምሕረትን አድይን ኪዳነምሕረት የዓለም መዳኛ
ስለቸርነትሽ እመቤቴ ለእኔ እናቴ ነሽ
ስለ ንግሥትነትሽም እመቤቴ ነሽ
ዝናባት ሳያጠጡት አየራትም ሳያሳድጉት
ሰማያዊ እንጀራ የሰጠሽን ቤተልሔማዊት
ቃና ዘገሊላ በሠርግ ቤት በዚያ ተገኝተሽ ሳለሽ
ውኃውን ወደ ወይን በአንቺ ምልጃ እንዳስለወጥሽ
ዛሬም የእኔ ሕይወት ወይኑ አልቆ ባዶ ሆኗልና
አንቺ የአምላክ እናት ንጽሕት ቅድስት ርኅርኂተ ኅሊና
ሕይወቴን ቀድሰሽ እመቤቴ ሙይው በምስጋና
Негізгі бет ጎሥዓ ልብየ ቃለ ሠናየ
Пікірлер: 1