ኢትዮጵያዊው ተማሪ በጣሊያን ሞ*ቶ ተገኘ
(እባካችሁ አስቸኳይ ነው ሼር ሳታደርጉ አትለፉ!)
***
የ22 ዓመቱ አቤኔዘር ተሰማ አበበ ስኮላርሺፕ አግኝቶ ጣሊያን፤ ሲሲሊያ ግዛት መሲና ዩኒቨርስቲ የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ የነበረ ሲሆን በትላንትናው ዕለት ማታ እንደተኛ ሞ*ቶ ተገኝቷል። የሞ*ተበትንም ምክንያት ፖሊስ እየመረመረ ይገኛል።
አስከ*ሬኑን ወደ ሀገር ቤት ለመምጣትም ወጪው ከፍተኛ ስለሆነና ቤተሰብ በታላቅ የልብ ስብራት ውስጥ ስለሚገኝ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጪ የምትገኙ ደጋግ ኢትዮጵያን እንድትረባረቡ በአክብሮት እንጠይቃለን።
የወላጅ እና የልጅ ወጉ ወልዶ አሳድጎ ለቁም ነገር አብቅት…በልጅ ልጅ ከብዶ ትውልዱ እንዲቀጥል በምርቃቱም በፀሎቱም እየረዱ ማክረም ነበር ….ልጅም ደግሞ ከወላጅ ትዕዛዝ ሳይወጣ …ተምሮ ተመራምሮ ለሀገርም ለወገንም እንዲበጅ ሁኖ አድጎ ..ወላጅ እጦረ …አይን ማረፊያቸው ሆኖ መኖር ነው፡፡
ወላጅ ወልዶ ያሳደገው ልጅ ቀቁም ነገር ሲበቃለት ከማየት የዘለለ ምንም ትርፍ የለውም …ሁሉ ሰው ልጆቹ አድገውለት ማትየ ይሻል …እንኳን እና በዕድሜ ገፍተው በስለው ቀርቶ … ገና ዕድሜያቸው ያን ያህል ባይገፋም እንኳ በለጋነታቸው ለጋ ለግላጋ ሆነው በቁመት ወላጆቻቸውን አክለው ሲታዩ እንኳ የወላጅ ደስታው ብዙ ነው፡፡
ታድያ መቼም የተፈጥሮ ህግ ነው እና እንዲህ በስስት የሚያዩአቸውን ልጆች …ሞት ይሉት ነገር መጥቶ ሲነጥቃቸው ይሆኑትን አኳኃን አለማየት ነው የሚበጀው፡፡ እሰየው ነው አደገልኝ …ደረሰልኝ …ደግሞ ተምሮ ተመራምሮ ሊመረቅልኝ ነው ብለው ነጋ ጠባ ልብ ሀሳብን ያልነጠሉበትን ልጅ ሞት ይሉት ክፉ ነገር መጥቶ ሲወስድባቸው ማየት ሕመሙን እንዲህ ነው ብሎ መግጥ አይቻልም ፡፡ እንዲህ ያለ ነገር የገጠማቸው ብዙ ሰዎች አይተናል ፡፡ በቅርቡ ድምጻዊት ዘሪቱ ከበደ የጠማነትን የልጅ ማጣት ፈተና ሁለችንም የምናስታውሰው ጉዳይ ነው፡፡ በአምላኳ ቃል በብዙ ተፅናናችን እንጂ ክስተቱ ቆሞ የሚያስኬድ አልነበረም፡፡ ደግሞ ወደ ኃላ ትንሽ ጊዜ መለስ ስንል እንዲሁ አንጋፋው ጋዜጠና እሸቱ ገለቱም እንዲሁ ለትምህርት አሜሪካን ሀገር የሄደች እጅግ ፍልቅልቅ ጎበዝ እና ታታሪ የሆነች ልጁን ተምራ ተመርቃ ትመጣልኛለች ብሎ በጉጉት ሲጠብቅ …እጅግ ልብ በሚሰብር መልኩ እስክሬኗን ተቀብሏል፡፡መሪር ሀዘኑንም በብዙ ሲገልጥ እና ሲታይበትም ሰንብቶ ነበር፡፡
ለብዙ ስትጠበቅ በአጭሩ አልፋ የተገኘችው የተማሪ ምስራቅ እውነቴንም ጉዳይ እንዲሁ የሚረሳ አይደለም፡፡
ዛሬም እንግዲህ ወደ ጣሊያን ተሰማ የተባለው ልብ የሚሰብረው ዜናም የዚሁ አይነት ነው፡፡
ይህ እዚህ ምስሉ ላይ የምትመለከተቱ ወጣ 22 ዓመቱ ነው አቤኔዘር ተሰማ አበባ ይባላል፡፡ ጎዝ ተማሪ ነበረ፡፡ስኮላር ሺፕ አግኝቶ ወደ ጣሊያን ሀገር ለተሻለ የትምህርት ዕድል ያቀናና በዚያም በሲሲሊያ ግዛት መሲና ዮኒቨርስቲ ገብቶ የኮምፒውተር ሳይንስ ትምህርቱን እየተከታተለ ነበር አሉ ፡፡ ታድያ ከትላንት ወዲያ ማታ እንዴት እና በምን ሁኔታ ውስጥ እንደተፈጠ ለጊዜው ባልታወቀ ሁኔታ ውስጥ ያ ጎበዝ የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ ከትላንት በስቲያ ሕይወቱ አልፋ አስክሬኑ መገኘቱ ተሰምቷል፡፡ ይህን ዜና ለቤሰብ ማርዳትም ሆነ እንደቤሰብ ሆኖ ጉዳዩን መስማት ልብን ዝቅ ያደርጋል፡፡ አቤኔዘር ተሰማ የሞተበት ምክንያት እስካሁን ምን እንደሆነ ባይታወቅም ...ፖሊስ ግን ጉዳዩን ይሁነኝ ብሎ ይዞ እየመረመረ ይገኛል፡፡
መቼም ብዙ ለፍተው ጥረው ይሆል …ይሳካል …ይይዝለት ይሰምረለታል ብለው እዚ ያደረሱ ቤተሰቦችም ቢሆኑ ቆሞ የሸኙትን ልጅ ሞቱ ሊቀበሉት ግድ ሆኗል፡፡ መቼም ልጅ ነውና አስክሬኑን አምጥተው …መከፈኛውንም …ሳጥኑነም ዳብሰው እያለቀሱም ቢሆን አፈር ማልበስ የአባት የእናት …እልፍ ሲልም የዘመድ አዝማድ ወጉ ነው እና …ዘመድ አዝማድ ሀዘናቸው ላይ አስክሬኑን ለማምጣት ደፋ ቀና ይሉ ይዘዋል፡፡
በብዙ አጋጣሚዎች እንደሰማይ እንዳየነው ከሆነ ደግሞ አስክሬን ከውጭ ማምጣት መከራው ብዙ ነው ፡፡ በዚያ ላይ ክፍያው ወገብ የሚቆርጥ በግለሰብ ደረጃ የማይቻል ነው ፡፡ እንኳን እና አስክሬንን ሀገር አሳብሮ …ሰማይ ሰንጥቆ …ሀገር አቋርጦ አምጥቶ ቀርቶ ሀገር ውስጥም ድንኳን ተክሎ ሀዘን መቀመጥ እንዲህ እሳት በላሰ ኑሮ የማይቻል ነው ….ለዚህ ነው እንግዲህ የዚህን ታዳጊ አስክሬን ካለበት ሀገር ለማምጣት እና ለሀገሩ አፈቀር ለማብቃት ተብሎ ጎ ፈንድሚ አካውነት የተከፈተው ፡፡
በጎ ፈንዱ አካውንነትም ላይ እንሆ እንዲህ የሚል የተማፅኖ መልዕክት ሰፍሯል
ሙሉ የትምህርት እድል አግኝቶ ከኢትዮጵያ ወደ ጣሊያን የተጓዘው እና ህልሙን ለመኖር በመጣር ላይ የነረው አቤኔዘር ተሰማ አበበ በድንገት በአሳዛኝ ሁኔታ ከዚህ አለም በሞት መለየቱን ስንሰማ እጅግ አዝነናል። አቤኔዘር ተሰማ አበበ ጎበዝ እና ተወዳጅ የማህበረሰባችን አባል ነበር።
የአቤኔዘር ተሰማ አበበን አስከሬን ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ እና ከወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር ለማሳረፍ የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን የእናንተን ድጋፍ እንፈልጋለን። ቤተሰቡ ይህንን የገንዘብ ሸክም ብቻውን ማስተዳደር አልቻለም የምትችሉትን ሁሉ አግዙን የሚል ነው፡፡
ታድያ በዚህ አጋጣሚ ሁላችንም ምን እንዴት እንደሚገጥመን አናውቅም እና አቅም በፈቀደ የተማሪ አቤኔዘርን አስከሬን ለሀገር ለምድሮ እንዲበቃ እና ቤተሰብም አፈር እንዲያለብሰው የበኩላችንን በምትመለከቱት የጎ ፈንድ ሚ አካውንት እናግዛቸው ዘንድ ተማፀንን፡፡ ያልቻልን ደግሞ በፀሎት ብናበረታቸው እሰየው ነው፡፡
gofund.me/0149...
Tessema Abebe
1000020084913
Commercial bank
(ልለምናችሁ ቢያንስ ለ10 ሰው ሼር አድርጉ!)(@gizemedia1974
Негізгі бет እጅግ ልብ ይሰብራል!የ22 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ተማሪ በጣልያን ሞቶ ተገኘ!(@gizemedia1974)Ethiopia|EliasDegenet|28 August 2024
Пікірлер: 127