በዛሬዉ ከውሸቱ ባሻገር ፕሮግራማችን፡ ሃሰተኛ መረጃ በተባበሩት መንግስታት ዘላቂ የልማት ግቦች ላይ ያመጣው ተፅዕኖ አለ ወይ?፣ አሁን ያለው የሀሰተኛ መረጃ ስርጭት ምን ይመስላል ቀንሷል ወይስ ጨምሯል?
የሀሰተኛ መረጃ ስርጭትና የጥላቻ ንግግርን ለመግታት እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ምን ይመስላሉ?
የሀቅ ማጣራት (fact-checking) ስራን ወደ Mainstream (መደበኛ) ሚድያዎች ላይ ማምጣት ጥቅሙ ምንድነው? ፣ በሀገሬ ቲቪ የሚተላለፈውን “ከውሸቱ ባሻገር” የሚለውን መርሐግብር እንዴት አያችኹት? ከቴክኖሎጂ መዘመን ጋር ተያይዞ የሀሰተኛ መረጃዎች የበለጠ እየረቀቁ ነው የሚሄዱት በተለይም ከAI (ሰው ሰራሽ አስተውሎት) እንደ አለም ወይም እንደ ሀገር ስጋት ውስጥ ነን ወይ? ከዚህ አንፃር ለሚድያዎች እና መረጃን ለሚያጣሩ ተቋማት ምንድነው የምትመክሩት? ስንል ከእንግዶቻችን አቶ አደራው ገነቱ በዩኔስኮ ውስጥ በኢትዮጵያ የኮምኒኬሽን እና ኢንፎርሜሽን ፕሮግራም ሀላፊ እንዲሁም አቶ ኤርሚያስ ሙሉጌታ (ከፍተኛ የሚዲያ ባለሙያ) ጋር ያደረግዉን ቆይታ ክፍል አንድ ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡
Негізгі бет ከእንግዶች ጋር የተደረገ ልዩ ቆይታ - ከውሸቱ ባሻገር
Пікірлер