ነፍስ ይማር የተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ዛሬ ስንዘክር በአለም አቀፍ ደረጃ እኔ በወጣትነት እድሜዬ ወደ ሰላማዊ ትግሉ ያመጡኝ ሲሆን ከመሰሎቻቸው ጋር መአህድ ( መላው አማራ ህዝብ ድርጅት ) አቋቁመው እኔም በአዲስ አበባ ቂርቆስ አውራጃ ወጣት ካውንስል አባልና የአውራጃው አመራር የወጣቶች ሆነን በአዲስ አበባ ወጣት ካውንስል ታቅፈን አገር አቀፍ ፓርቲ ለመሆን በሚደርገው ጥረት ፓርቲው የተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን የምርጫ ቦርድ ቢያንስ ከ5ክልል ከአንድ ሺ አምስት መቶ(1500) አባል ፊርማ ማቅረብ አለባቹሁ በሚል ስለተጠየቀ እኔም ትውልድ አገሬ ሃረር ከተማ ይህንን ማከናወን ይቻላል ብዬ በወቅቱ ሃረር ክልል 13 በሚል ተዋቅራ ስለነበር እሳቸውም ነፍስ ይማር ቀጥል ሂድ ብለው ሃረር ሄጄ ወቅቱ በጣም የከፋ አማራው የሚገደልበት ፣ የሚሰወርበት ፣ ብዙ መከራን የሚይበት ከመሆኑም በላይ በበደኖ እንቁፍቱ በሂወት ወደ ጉርጎድ ተጥለው የተገደሉበት በጃራ አባገዳ በሚመራው እስላሚክ ኦርምያ ነጻ አውጪ አይፌልኦ(IFLO) በሚባለውና የወያኔ ኢህአዲግ አውሮራ ክፍለ ስራዊት በሚመራው ሳሞራ ዩኒስና ዛሬ በሂወት የሌለው ሳእረ መኮንን ከጃራ ጋር ሆነው ወንጀሉን ለኦነግ ለማሸከም በማሴር ይህንን ስል ኦነግ ቅዱስ ነው ለማለት ሳይሆን በወቅቱ ጃራ ከወያኔ ጋር ወግኖ ኦነግን ሃረርጌ ውስጥ እየተዋጉ ስለነበር በጥምረት ይህንን ኦፕሬሽን ከወያኔ በኩል ታደሰ ቻይና የተባለ የገዳይ ቡድን አሰማርቶ በእራሳቸው ካሜራ ማን ቀረጻ በማዘጋጀት ከቀድሞው ነብስ ይማር ጀነራል ደምሴ ቡልቶ መኖሪያ ሳእረ ስለሚናርበት ሳሞራም ከአዲስ አበባ ሲመጣ ከሚርፍበት ቤት የሄደው ገዳይ ቡድን የሄዱበት መኪኔ ዶጅ ሲር ኮርተር ሽሮ ከለር የአሜሪካን ወታደሮች ጎልፍ ላይ የተጠቀሙበት አይነት በሆነ ወደ ኩራፋ ጨሌ ተጉዘው በደኖ እንቁፍቱ ላይ አሳዛኙን ግፍ ፈጽመዋል ይህንን በአይን እማኝ በሚዲያ መስክሬለሁ በዚህ ሁኔታ ከፍተኛ ስጋት ቢኖርም በአማራው ላይ ሃረር ግን በዚህ በለመበገር ጽፈት ቤት ከከፈቱ ክልል ሆነ ከተሞች በተሻለ በሁለት ቀን ጊዜ እቤት ለቤት በመዞር በቁጥር 2500(ሁለት ሺ አምስት መቶ አባል) አስፉርመን ዝርዝሩን ለድርጅቱ አምጥተናል በዚህ ድንቅ ስራ የተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ በወቅቱ ጽፈት ቤት በለን ከተሞች ይህ አልሆነም ብለው ለእኔም ሆነ ለሃረር ህዝብ አጋርነት ከልብ በስብሰባ አመስግነዋል ፓርቲውም በምርጫ ቦርድ ተገቢውን ፎርማሊቲ ስላሞላ ወደ አገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲነት ተሸጋግሮ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ትያትር በተዱረገ ጉባዬ ይፋ ሆኖል እኔም የሃረር ከተማና አካባቢን ወክዬ በጉባዬው መልክቴን አቅርቢለሁ ይህ ህያው ምስክር ነው ።
የተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ጋር ከዚህ አለም በሂወት እስከ ተለዩ በአጋርነት ቀጥያለሁ ታስሬለሁ ፣ ብሎም ብዙ መከራን ተቀብያለሁ ቤት ንብረቴን ብሎም የግል መኪናዬን ተነጥቄለሁ ከህግ ውጪ ነፍስ ይማር የተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አስክሬን ከአሜሪካን መቶ ከቦሌ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ለማድረስ በምሽት አጅበን ብዙ ህዝብ ተሰባስቦ መፈክር እያልን ወድ ለገሃር ጉምሩክ አጠገብ ወደ ሚገኘው ቤታቸው ስናመራ እሳታዲዮም እስፖርት ፌዴሬሽን ፊት ለፊት ስንደርስ በአምስት ማክ የመጣ አጋዚ ከፍተኛ ጭፍጨፋ ፈጽሞ የቻለውን እየጫነ ሲግዝ እኔ እና ጥቂቶች የአስክሬን መኪናውን በመያዝ ለመትረፍና እቤታቸው እስከ ለሊቱ ስምንት ሰአት ለመቆየት ተገደናል በማግስቱ የአስክሬን ሽኝት ላይ በመገኘት የሃረር ከተማን በመወከል የአበባ ጉንጉን በቤተክርስቲያን አኑረናል ከቀብር ስነስርአት ከተፈጸመ በሆላ ወጣቱ አስራት አልሞተም አስራት አልሞተም በሚል ከፍተኛ ድምጹን እያሰማ በእየአደባባዩ እየጮኸ ሲወጣ ከፓርላማ ጥበቃ በተኩስ እሩምታ አንድ ወጣት ሂወቱ አልፎል እውነት ነው የተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አልሞቱም የቆሙለት የሰላማዊት ትግል እስከ ቅንጅት ዘልቆ በቅንጅት ውስጥ ከፍተኛውን የፓርቲ አባላት ከአቀረቡ ድርጅቶች ትልቁን ቁጥር የያዘው መኡህድ (መኢአድ ) ነው ሰላማዊ ትግሉ አሸነፈ ዛሬ የተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አላማን ያነገበውን ፋኖን ወለደ እውነትም አስራት አልሞቱም የአስራት ልጆችነን ይላል ፋኖ ፋኖ ፋኖ ።
ይህንን ቀን ስንዘክረው ነብስ ይማር ከተከበሩ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ጋር ሆነው ዋጋ ለከፈሉ ኡርበኞች ትግሉን እስከ ቅንጅት እንዲጎዝ ላደረጉትን ለኢንጂነር ሃይሉ ሻውል ጭምር ክብር ይታሰባሉ እነሱን ትውልድ ምንጊዜም ይዘክራል የታሪክና የህዝብ የሰንደቃላማ ብሎም የዘር የብሄር የአንድነት የእምነት ጠላቶችን ታግሎ በስም ሆነ በሚገባው ሁለገብ ትግል አስተባብረው አቀናጅተው ለዚህ ትውልድ የአያቶችህን የአባቶችህን አገርና ህዝብ ታሪክ ጠብቅ ብለውታል ክብር ለሚሰጠው ክብር እንሰጣለን ከመሰሎቼ ጋር ይህንን ለአስተባበራቹሁ ይህንን ቀን እንዲዘከር ከልብ እናመሰግናለን የዚህ ትልቅ ታሪካዊ ትግል ተሳታፊ በመሆኔም ኩራት ይሰማኛል ክንዴን ሳልንተራስ የእነ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ እና መሰሎቻቸውን አላማ ከግብ ለማድሩስ ከእግዚአብሔር ጋር የዜግነት ድርሻዬን እወጣለሁ ሞት ለባንዳ ሹንባሽ ዱቄት ተሸካሚ ።
ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቾ ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኖራለች ይህንን መፈክር ነብስ ይማር ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ይሉት ነበር ምንጊዜም እውነት ነው ።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያና ህዝቦቾን ይባርክ ይጠብቅ
ቅዱስ ሚካኤል እኛንም በያለንበት ይጠብቀን ጠላቶቻችን በስይፉ ጎምዶ ይጣልልን ይህንን ብያለሁ አሜን ቸር ይግጠመን።
#asham_news #benegerachin_lay #eritrean_sitcom_comedy #abelbirhanu #addis_ababa_documentary #ethiopian_music_tigrigna_new #ethiopian_bloggers #fetadailynews_derene #ethiopianair_force_show
Негізгі бет ለመዐህድ ከመታገል የፕ/ር ቀንን ለማክበር እስከመድረስ
Пікірлер