መቁጠርያ ማለት ምን ማለት ነው?፡፡ መግረፍያ ማለት ነው፡፡ 41 ወይም 64 ነው፡፡ 41 የሚሆነው የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር በ40 ዓመት ቁጣዉን አቆመና በ41ኛው ዓመት ወደ ቅድስት አገር አስገባቸው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ 40 ቀን ፆመና በ41ኛው ቀን የዲያብሎስን ሰራዊት አሸነፈው፡፡ ስለዚህ 41 ይሆናል ማለት ነው መቁጠርያ፡፡ ይሄ ነው ታሪካዊ ዳራው ወይም በታሪክ አቅጣጫ የመጡበት፣ የሄዱበት የፈለጉት አባቶቻችን መንገድ በመቁጠርያው ረደግ ይሄ ነው፡፡ 64 የሚሆነው የእመቤታችን ዕድሜ ነው፡፡ እመቤታችን 64 ዓመት ኖረች በመጨረሻ ዓረፈች፡፡ ከሙታን ተለይታ ወደ ሰማይ አምላክ አርጋለች፡፡ ስለዚህ ያረገች የእመቤታችንን መንፈስን በረከት በዕድሜዋ ላይ ያገኘችዉን ጸጋና ተስፋ፣ በሕይወት ውስጥ ያሳለፈችው ራዕይና ኃይል ለማግኘት 64 ይሆናል በእመቤታችን ዕድሜ፡፡
መቁጠርያ በመሰረቱ ቃሉ መ-ቁ-ጠ-ር-ያ ነው ራሱ ቃሉ፡፡ አባቶቻችን ማንበብ ስለማይችሉ እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስን 41 ግዜ፣ ይቆጥራሉ፣ በእንተ ማርያም መሐረነ ክርስቶስን 41 ግዜ፣ ኪላላይሶን ክርስቶስን 41 ገዜ፣ አምላኬ አምላኬን 41 ግዜ፣ ስምዓነ አምላክነ 41 ግዜ፣ አድህነነ ከመዓቱ ይሰውረነ በምህረቱ ምእንተ ማርያም ወላዲቱን 41 ግዜ፡፡ እንደዚህ እያደረጉ ይጸልዩና ከዚህኛው ዘመን ትውልድ ለየት የሚሉት አንዳንድ መናፍስት በሕይወታቸው ውስጥ እንዳይገባ ትከሻቸዉን፣ ጀርባቸዉን፣ ማጅራታቸዉን፣ ራሳቸዉን፣ እግራቸዉን፣ ባታቸዉን፣ ሆዳቸዉን፣ ክንዳቸዉን በመቁጠርያው ይመቱታል፡፡ የሚመቱት ጥልቅ የሆነ የመንፈሳዊ ሕይወት ግንዛቤ ስላላቸው ነው፡፡ የሚመቱት ክፉ መናፍስት ጸሎታቸዉን እንዳያስታጉል፣ ድካም እንዳያመጣባቸው፣ እግራቸዉን እንዳይይዝ፣ ቁርጥማት እንዳይሆን፣ የብርድ በሽታ እንዳይሆን፣ ነርቭ እንዳይሆን ግንዛቤ ስላላቸው ነው የክፉ መንፈስ፡፡
ሌላው ደግሞ ውስጣቸዉን እንዳያዝ፣ የሚሰሩትን ሥራ እንዳያበላሽባቸው፣ የሚያዩትን እርሱ እንዳያይ፣ የሚሰሩትን እርሱ እንዳይሰራው ነው የሚመቱት፡፡ በኋላ መውረር፣ ማቃጠል፣ መብላት በሰውነት ውስጥ መሄድ፣ እንደ ድንጋይ መሆን በአካላቸው ሲሰማቸው መንፈሱ እንደገባ መረጃ ያገኛሉ ማለት ነው፡፡
ይሄ በጣም ልዩ ላብራቶሪ ነው፡፡ በዚህ መሰረት አሀ ይሉና ለምን ሰውነቴ ስመታው አላመመኝም ወይም ለምን እንዲሰማኝ አልሆነም ብለው በደንብ አድርገው ሲመቱት ራሱ ከዛ መረጃ ይሰጣቸዋል፡፡ ማን ነው የገባሀው ብለው ሲጠይቁት እኔ ነኝ፣ ልክፍት ነኝ፣ የምትሸነፍ መስሎኝ ነው የገባሁት፣ የማታውቀኝ መስሎኝ ነው የገባሁት፣ ቡዳ ነኝ፣ ዓይነጥላ ነኝ ብሎ ይነግራቸዋል፡፡ ወድያው በዛ ይቀጠቅጡት ይቀጠቅጡትና ወደ ግንባር ላይ ያስሩታል፡፡ ግንባር ላይ ይታሰርና አብሮ ይሰግዳል፡፡ ከዛ በኋላ አልፈልግም ብሎ ለራሳቸው ሸኘኝ ብሏቸው አልያም ደግሞ ነግሯቸው በቃ መሄዴ ነው አልቻልኩም፡፡ እንዴ ለካ እንደዚህ ነህ አንዴ፣ ይሄን ያል ጠንካራ ነህ እንዴ፣ ይሄን ያህል ከእግዚአብሔር ጋር የኖርክ ነህ እንዴ ብሎ ለቋቸው ይሄዳል፡፡ ስለዚህ መቁጠርያው በየዋህነት የሚጠቀሙበት የእምነት የጦር ዕቃ ነው፡፡
Негізгі бет Memhir Girma መምህር ግርማ ወንድሙ ክፍል 2 ስለ ፀሎት ቤት ስለ ስግደት ስለ መቁጠርያ አጠቃቀም ሰምተን መክሊታችንን ለሌሎች በማሰማት እናትርፍ ሼር
Пікірлер: 98