ቅድስት (፪ኛ ሳምንት)
ወንጌል፡- ማቴ ፮.፲፮-፳፭
‹‹በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ፡፡ እነርሱ እንደ ጾሙ ሰው ያውቃቸው ዘንድ ይጠወልጋሉና፤ ግንባራቸውንም ይቋጥራሉና መልካቸውንም ይለውጣሉና ፡፡ እውነት እላችኋለኁ ዋጋቸውን ተቀበሉ፤ እናንተስ በምትጾሙበት ጊዜ ራሳችኹን ቅቡ፡፡ ፊታችኹን ታጠቡ እንደ ጾማችኁ ሰው እንዳያውቅባችኁ የተሰወረውን ከሚያውቅ በሰማይ ካለ አባታችኁ በቀር በስውር የሚዐያችኁ አባታችኹም ዋጋችኹን በግልጥ ይሰጣችኋል፡፡የሚያልፈውን፣ ብል ነቀዝ የሚያበላሸውን ሌቦች ቆፍረው የሚሰርቁትን ምድራዊ ሀብት አትሰብስቡ፡፡ የማያልፈውን የማይጠፋውን፣ ብል ነቀዝ የማያበላሸውን፣ ሌቦች ቆፍረው የማይሰርቁትን ሰማያዊ ሀብትን ሰብስቡ እንጂ፡፡ ገንዘባችኁ ካለበት ልባችኹም ከዚያ ይኖራል፡፡ የሥጋኽ መብራቱ ዐይንኽ ነው፤ዐይንኽ ብሩህ ከኾነ መላ ሰውነትኽ ብሩህ ይሆናል፡፡ ዐይንኽ ታማሚ ከኾነ ግን መላ ሰውነትኽ ጨለማ ይኾናል፤ በአንተ ላይ ያለው ብርሃን ጨለማ ከኾነ፤ ጨለማኽ እንዴት ይኾን? አንድ ባርያ ለኹለት ጌቶች መገዛት አይችልም፡፡ ያለዚያ አንዱን ይወዳል አንዱን ይጠላል፤ ያለዚያም ለአንዱ ይታዘዛል ለኹለተኛው እንቢ ይላል፤ እናንተም ለእግዚአብሔር እና ለገንዘብ መገዛትን አትችሉም፡፡››
ዋናው መልዕክት፡-
•በመላእክት እና በሰዎች የተመሰገነ እግዚአብሔር ሃይማኖትና መልካም ተግባር ያላቸው ሰዎችን ይወዳል፤ ሰማይንም የፈጠረ እርሱ ነው፡፡
•ክርስቲያን ምግባረ ሃይማኖቱን በሚፈጽምበት ጊዜ መሰቀቅ መድከምም አይገባውም፡፡ በፍቅር፣ በአንብአ ንስሐ፣ በጸሊዓ ንዋይ፣ በምፅዋትም መፈጸም ይገባዋል፤
ተጨማሪ መልእክት፡-
•ችግረኞችን በገንዘብም ኾነ በሌላ ትሩፋት መርዳት ሰማያዊ ሀብትን ማድለብ ስለ ኾነ ዋጋውም ታላቅ በመኾኑ በደዌና ርሱ ባስከተለው ችግር ላይ የወደቁ ወገኖችን ለመርዳት እና ለማስረዳት እንበርታ፡፡
‹‹ለጽድቅ አድሉ፤ ባልንጀራችኹን ውደዱ፤ የምትራሩም ኹኑ፡፡›› ሮሜ. ፲፪.፲፣ ኤፌ. ፬.፴፪
• /መዝሙር ዘቅድስት ግነዩ ለእግዚአብሔር/
፩ኛ ተሰ ፬. ፩.፲፫
፩ጴጥ ፩.፲፫
ዮሐ.ሥ.፲.፲፯-፴
ምስባክ መዝ ፺፭.፮
እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ
ትርጉም ፡-
እግዚአብሔርስ ሰማያትን ፈጠረ፤
ሃይማኖት ምግባር በፊቱ ነው፤
ቅድስና ከምስጋና የሚበልጥ ምስጋና በመቅደሱ አለ፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ለዓለመ ዓለም አሜን!!!
ምንጭ
ቃለ ሕይወት በሊቀ ትጉኀን ኀይለ ጊዮርጊስ ዳኘ
ሰባቱ አጽዋማት በተስፋዬ ምትኩ
Негізгі бет 🛑 ምስባክ ቅድስት (፪ኛ ሳምንት) - በአባ ገብርኤል
Пікірлер: 3