ይሔን ቻናል #subscribe በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ! / @17mediia
ምሥጢረ ስጋዌ | የአምላክ ሰው መሆን
ሥጋዌ ተሰገወ ሰው ሆነ ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ምሥጢረ ሥጋዌ ማለት ሰው የመሆን ምሥጢር ማለት ነው::
አምላክ ለምን ሰው ሆነ?
1. አዳምን ከበደል ሊያነጻው
አዳም የሰይጣንን ምክር በመስማት እግዚብአሔር አትብላ ያለውን ዕፀ በለስ በልቶ ትእዛዙን በማፍረሱ ከፈጣሪው በተጣላ ጊዜ የሞት ፍርድ (ሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ) ተፈረደበት ። ዘፍ 3፥1 ። ለጥፋቱ ምክንያት የነበሩት ዕባብና ሄዋንም እንደ ጥፋታቸው መጠን ተረግመዋል ። ዘፍ 3፥14 ።
አዳምም ጥፋቱን አምኖ ንስሓ ስለገባ አምላክ ሰው ሆኖ እንደሚያድነው ቃል ገባለት ። ዘፍ 3 ፥ 22 ። ቃል ኪዳኑም “አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ” የሚለው ሲሆን እግዚአብሔር ወልድበተለየ ስሙ ፣ በተለየ ግብሩ ፣ በተለየ አካሉ ፣ ሰው ሆኖ እንደሚ ያድነው ቃል መግባቱን ይገልጻል። ለአዳም በገባው ቃሉ መሰረት ጊዜው ሲደርስ ከተፈረደበት ፍርድ ነፃ ሊያወጣው (ሊያድነው) ሰው ሆነ ። ገላ 4 ፥ 4 ። ጊዜው ማለት አምስት ሺህ አምስት መቶ (አምስት ቀን ተኩል ሲፈጸም) ማለት ነው ። መዝ 84 ፥ 4 ።
2. የሥጋን በደል ለመካስ
አዳም ፤ ዕፀ በለስን በበላህበት ቀን ሞትን ትሞታለህ (ዘፍ 2፥ 17) ያለውን አምላካዊ ቃል ተላልፎ በለስን በመብላቱ የሞት ፍርድ ከተፈረደበት በኋላ ንስሃ በመግባቱ አምላክ ትሞታለህ ያለው ፍርዱ ሳይሻር ይቅር ይለው ዘንድ ወደደ ። በመሆ ኑም በመለኮታዊ ባህርዩ ሞት ስለማይስማማው የሚሞት ሥጋን ለብሶ (ሰው ሆኖ) ቅጣቱን ሊቀበልለት ። ኢሳ 53፥1 ። የእግዚአብሔር ቸርነቱ የባህርዩ ስለሆነ ሞቱን ሞቶ ፍርዱን በመፈጸም ይቅር ብሎ ቸርነቱን በማድረግ ፍርዱንም ይቅር ባይነቱንም በአንድ ጊዜ ሊገልጽ ፈቃዱ ስለሆነ
3. ፍቅሩን ለመግለጽ
እኛ ሰዎች ምንም ያህል ሰውን ብንወድ ቁሳዊ ነገር ልንሰጥ እንችላን ። እርሱንም ቢሆን ጥቅማችንን (ትርፋችንን)አይተን ነው ። አምላካችን ግን ከእኛ ምንም ላያገኝ ባህርዩን ዝቅ አድርጎ ደካማ ባህርያችችንን በመዋሃድ በአዳም የተፈረደውን ፍርድ እርሱ ተቀብሎ በማዳን እውነተኛ ፍቅሩን ሊገልጽልን ስለወደደ ።
#ዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ #Deacon_Henok_Haile #Deyakon_Henok_Haile #janderebaw #henok_haile #henokhaile #henok #ethiopia #eotc #sibket #ስብከት #tinsae #ethiopia #fasika #ትንሳኤ bible stories amharic | amharic bible audio new testament | orthodox preaching amharic | ethiopian orthodox prayer in amharic | orthodox preaching | ethiopian orthodox mezmur jesus | ethiopian bible history | ethiopian orthodox explained | ethiopian preaching | orthodox prayer life | ethiopian spirituality | Orthodox bible stories
Негізгі бет ምሥጢረ ስጋዌ | የአምላክ ሰው መሆን | ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ | Dn. Henok haile
Пікірлер: 1