ሕይወት ያለ ዓላማ እና ያለ ተልዕኮ ትርጉም አልባ ነው። ሥልጣን ቢኖረን፣ ሀብት ብናካብት፣ በዕውቀት ብንልቅ በዝና ብንጥለቀለቅ የምንኖርለትና የምንሞትለት ዓላማ ከሌለን ኑሮ ጣዕም አይኖረውም። እግዚአብሔር የዓላማ አምላክ ነው። ዘላለማዊ ዓላማውን ተልዕኮ አድርጎ ሰጥቶናል። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋ ለብሶ የመጣለት፣ በመስቀል ላይ የሞተበት፣ ሞትን አሸንፎ ተነስቶ በግርማው ቀኝ የከበረለት ዋና ዓላማ ከነገድ፣ ከቋንቋ፣ ከወገን ሁሉ ሰዎችን ደቀ-መዝሙር ማድረግ ነው። በሌላ አገላለጽ እሱን የሚመስሉ ልጆች ማፍራት ነው። ይህ ታላቅ ተልዕኮ የተሰጠው ለታላላቅ ሰዎች ሳይሆን ለደካሞች ነው። ምክንያቱም የሚፈጸመው በኃይልና በብርታት ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነው። ታዲያ ይህ ታላቅ ተልዕኮ ምን ያህል ገብቶናል? በማቴ. 28፥16-20 የሚገኘውን የጌታ ቃል፣ የቃሉ መምህር ወንጌላዊ ያሬድ ጥላሁን በዝርዝር ይተነትነዋል። ያድምጡ፣ ያሰላስሉ፣ ይለወጡ። የምሥራቹ ለብዙዎች እንዲደርስ ያጋሩ፣ በየጊዜው ትምህርቶችን ለማግኘት ሰብስክራይብ ያድርጉ።
www.goldenoil.org
info@goldenoil.org
Негізгі бет ተልዕኮ መር ሕይወት
Пікірлер: 61