በቀራንዮ የተከፈለልኝ ውለታ/፪/
በምን አንደበት ይነገራል።
የአምላኬ ፍቅሩ ይደንቃል።
እንደ ወንጀለኛ በሸንጎ ፊት ቆመ።
ደዌያችንን ወስዶ ሕማም ተሸከመ።
በሸላቾቹ ፊት እንደ በግ ተቆጥሮ።
ሕያዋን አረገን ሞትን በሞት ሽሮ።
በቀራንዮ የተከፈለልኝ ውለታ/፪/
በምን አንደበት ይነገራል።
የአምላኬ ፍቅሩ ይደንቃል።
በደል የሌለበት በመስቀል ላይ ዋለ።
በጽድቅ የሚፈርደው ወንበዴ ተባለ።
በቀራንዮ አምባ ታየ እርቃኑን።
የተራቆትነውን ጽድቅ ሊያለብሰን።
በቀራንዮ የተከፈለልኝ ውለታ/፪/
በምን አንደበት ይነገራል።
የአምላኬ ፍቅሩ ይደንቃል።
እንዴት ይገለጣል ነገረ መስቀሉ።
መድኃኒት የሆነ ለዓለሙ ሁሉ።
መተኪያ የለውም ስቃይ ግርፋቱ።
ኤልሻዳዩ ጌታ ለባሪያው መሞቱ።
በቀራንዮ የተከፈለልኝ ውለታ/፪/
በምን አንደበት ይነገራል።
የአምላኬ ፍቅሩ ይደንቃል።
#AbelBegena
Негізгі бет Музыка የበገና መዝሙር መምህር ዲ/ን አቤል ተስፋዬ | Abel Begena
Пікірлер: 18