የውጭ ባንኮች፣ በኢትዮጵያ በባንክ ዘርፍ የሚሳተፉበትን አግባብ የሚዘረዝር “የባንክ ሥራ ረቂቅ ዐዋጅ” ተዘጋጅቶ ይፋ ኾኗል።
የዐዋጅ ረቂቁ፣ የውጭ ባንኮች፣ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ በባለቤትነት የሚይዙትን ተቀጥላ ወይም ቅርንጫፍ ለመክፈት ፈቃድ እንደሚያገኙ ይደነግጋል።
ይኸው ረቂቅ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ በዛሬ ኀሙስ ስብሰባው ላይ ውይይት ከሚያደርግባቸው የዐዋጆች ረቂቆች መካከል አንዱ እንደኾነ ተጠቅሶ የነበረ ቢኾንም ውይይት አልተደረገበትም።
መንግሥት፣ የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ለማድረጉ የተለያዩ ምክያቶች መኖራቸውን የሚያስረዱት የምጣኔ ሀብት ጉዳዮች ተንታኝ አቶ አማንይሁን ረዳ፣ በዘርፉ የውጭ ባንኮች ተሳትፎ አስፈላጊ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡ ኾኖም፣ የውጭ ባንኮች ከሀገር ውስጥ ባንኮች ጋራ ተቀናጅተው ካልሠሩ አሉታዊ ተጽእኖዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ስጋታቸውን ጠቁመዋል፡፡
ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።
- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -- - - - - - - - - -
🔷 የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ሊንኮችን በመጫን ይከተሉን።
ፌስቡክ - / voaamharic
ኢንስታግራም - / voaamharic
X - / voaamharic
ዌብሳይት - amharic.voanew...
የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ፡- / voaamharic
☎️የስልክ መሥመራችን 202-205-9942 የውስጥ መሥመር 14 ነው።
📡 ቪኦኤ-አማርኛ ስለ ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ አፍሪካ፣ ዩናይትድ ስቴትስ እና ዓለም አቀፍ በዲጂታል፣ በራዲዮና በቴሌቪዥን ዜናና ዘገባዎችን ለአድማጭና ለተመልካች ያቀርባል።
VOA Amharic reaches our audience on digital, radio, and TV, delivering news and content about Ethiopia, Eritrea, Africa, and the United States. We will also be bringing you Health Shows, Youth Shows, Democracy Field, Women’s Shows, and Sports Shows on different days, stay tuned.
Негізгі бет የውጭ ባንኮች በኢትዮጵያ ሊሠሩ የሚችሉበትን ድንጋጌ የያዘ የዐዋጅ ረቂቅ ይፋ ኾነ
Пікірлер