Source Face book: ቅድስት አርሴማ ደጓ እናቴ
“ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም።”ማቴ፡፬፥፬። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕደ ዮሐንስ፥ በፈለገ ዮርዳኖስ እንደተጠ መቀ፥ ልዋል ልደር ሳይል፥ ዕለቱን ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ሄዷል። በዚያም ከቆመ ሳያርፍ፥ ከዘረጋ ሳያጥፍ፥ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ጾመ። ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ፦ «መንፈስ ጌታችን ኢየሱ ስን ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፤» ብሏል። ይህም፦ መንፈስ ቅዱስ ሰማዕታትን አነሣሥቶ ወደ ደም ፥ ጻድቃንን አነሣሥቶ ወደ ገዳም እንደሚወስዳቸው አይደለም። ወንጌላዊው፦ መንፈስ፦ ያለው ፈቃዱን ነው። ምክንያቱም ከአብ ጋር በፈቃድ አንድ እንደሆኑ ሁሉ ከመንፈስ ቅዱስም ጋር በፈ ቃድ አንድ ናቸውና ነው።
ጌታችን፦ ወደ ገዳም (ወደ በረሀ) የሄደው ለወጣንያንም ለፍጹማንም አብነት ለመሆን ነው። በገዳም፦ ለወጣንያን ፆር ይቀልላቸዋል ፥ ለፍጹማን ደግሞ ይከብድባቸዋልና ነው። ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፦ ተክልና ውኃ ከማይገኝበት በረሀ ሆኖ የጾመው፦ መብል ለኃጣውእ መሠረት እንደሆነ ፥ ጾም ለምግባር ለትሩፋት መሠረት፥ ዲያቢሎስንም ድል ለመንሣት ኃይል እንደሆነ ለማሳየት ነው። ቅዱስ ያሬድ፦ ጾምን፦ «እማ ለጸሎት፥ ወእኅታ ለአር ምሞ፥ ወነቅዓ ለአንብዕ፥ ወጥንተ ኲሉ ገድል ሠናይት፤ጾም፡- ለጸሎት እናቷ፥ ለዝምታ እኅቷ፥ ለዕንባ ምንጯ፥ ለመልካም ገድል ሁሉ ጥንቷ (መሠረቷ) ናት፤» ብሏል።
ጌታችን፦ ከጾሙ በኋላ ተርቧል፤ መራቡም፦ የፈቃድ ረሀብ እንጂ እንደ እኛ የግድ ረሀብ አይደለም፤ በተዋሕዶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ የሆነ አምላክ፥ ረሀብ የሚስማማውን የሥጋ ባሕ ርይ እንደተዋሐደ ለማጠየቅ ተረበ። ከተዋሕዶ በኋላ ሁለትነት ስለሌለም አምላካችን ተራበ እንላ ለን።
facebook.com/permalink.ph...
Негізгі бет የምድረ በዳው ፈተና : መምህር ሳሙኤል አስረስ
Пікірлер: 32