መንፈሳዊ ንፅህናችንን የምንጠብቅባቸው መንገዶች
❶. ለእግዚአብሔር በንጹሕ ልብ በመገዛት
❷. ዲያብሎስንና ሰራዉን በመቃወም
❸. ነዘህላልነትን በማስወገድ
. . .
"እንግዲህ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል" ( ያዕ4 ፥7 )
ነገሩ እንዲህ ነው. . .
▹ ቆሻሻ ከሆንክ ዝንብ፣ አበባ ከሆንክ ደግሞ ንብ መሳብህ አይቀርም። ሁሉም ወደሚመለከታቸው እያሸተቱ ይሄደሉ። የትም ብትሆን ላንተ ማንነት የሚስማማ ወደ ሕይወትህ ትስባለህ። መልአክም ቢሆን ሌላም ቢሆን። የምትፈልገው ነገር በሕይወት እንዲኖርህ የዛ ነገር ምንጭ የሆነውን አካል የሚወደውን ይዘህ በመገኘት ወደ ሕይወትህ ሳበው። በእርግጠኝነት ይጎበኘሃል።
▹ አበባ ከሆንክ በንብ የሚመሰሉ ሁሉ ማለትም የበጎ መዓዛ ሁሉ ምንጭ የሆነው እግዚአብሔርን ፣ ቅዱሳንን፣ ጻድቃንን፣ ሰማዕታትን ወዳንተ ይመጣሉ። በአጭሩ የድል አድራጊዎች ማህበር ድግስ ባንተ ቤት ይደገሳል። ቆሻሻ (ኃጢአት) ይዘህ ከተገኘህ ደግሞ የዛ ነገር ባለንብረት ሰይጣን ይጎበኝሃል። ቤቱም ያደርግሃል። ስለዚህ ንጽህና መቅደስህን ጠብቅ።
Subscribe ማድረግ አይርሱ።👇
@ZemaAkotet
Негізгі бет 💥 የነፍስ ንጽሕና - በአባ ገብረ ኪዳን
Пікірлер: 21