ሰአሊው እስራኤል ማታ በሰላም ተኝቶ ጠዋት ለመነሳት ሲሞክር እግሮቹ መራመድ አልቻሉም። መቆም አቃተው መንቀሳቀስ ዳገት ሆነበት። ከዛን ጊዜ ጀምሮ እንደልቡ መንቀሳቀስ የማይችል ቤት የሚውል ሰው ሆነ ጀግናዋ ሜሮን ግን መነሳት እንደማይችል እያወቀች ሀገር ምድሩ እየተሳለቀባት ፣ ወንድ አጥታ ነው እያላት አገባችው። እንሆ ይህ ከተፈጠረ ድፍን 20 አመታት ተቆጠሩ። ሰዎች ውሀ ቀጠነ ብለው በሚፋቱበት ዘመን እነሱ 20 አመት እንደወርቅ በእሳት የተፈተነ የፍቅርና የትዳር ጊዜ አሳለፉ። ጌታ ኢየሱስ በትዳራቸው እየከበረና እየተከበረ እዚ ደረሱ። ክርስቲያን ፖድካስት ከስቱዲዮ ወጣ ብሎ ከእነዚህ ወርቅ ሰዎች ጋር በደሳሳ ግን ፍቅር በሞላው ጎጇቸው ተገኝቶ የበአል ቆይታውን አድርጓል ተመልከቱ።
Негізгі бет ያለ ልጅ በ20 አመት ትዳር በፍቅር ብቻ ኖርን |የአርቲስት እስራኤልና የሜሮን የሚገርም ምስክርነት|
No video
Пікірлер: 72