ዘፈን እና መዝሙር
በኦርቶዶክሳዊ ተዋህዶ ቤተክርስትያን አስትምህሮ መሰረት ዘፈን መስማት ፣ መዝፈንም ሆነ በዘፈኑ መጨፈር የተከለከለ ነው ።ይህም የሆነው በሚከተሉት ምክነያቶች ነው።
❖ ዘፈን የአጋንንት ሥራ ነው:: የአጋንንት ግብራቸው ዘፈን መዝፈን ነውና:: መጽሐፍ ቅዱስ ስለዘፈን በግልፅ አነጋገር እንዲህ ይላል "በዚያም አጋንንት ይዘፍናሉ" በማለት ስለ አጋንንት ዘፋኝነት ይናገራል::(ኢሳ.13:2
1) ። አትዝፈኑ ማለት የአጋንንትን ሥራ አትሥሩ ማለት መሆኑን መረዳት አለብን:: ይህን በተመለከተ መጽሐፈ መቃብያን ደግሞ እንዲህ ይላል:- ".እየዘፈኑም ከአጋንንት ጋር ይጫወቱ ነበር:: አጋንንትም ጫወታቸውንና ዘፈናቸውንም ሁሉ ያደንቁላቸው ነበር::" (1ኛ.መቃ.36:27-28) በዚህ ስፍራ አገላለጥ ደግሞ ለየት የሚለው አጋንንት ዘፋኞች ብቻ ሳይሆኑ ከዘፈን አድናቂዎች ጐራ መሰለፋቸው ነው::
❖ ታላቁ የቤተክርስትያናችን የስረአት መፅሐፍ ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ ሥራን አስመልክቶ ሲናገር እንዲህ ይላል:- "ስለ ተግባረ ዕድ ግን በዓለም ከሚሠሩ ሥራዎች መንፈሳዊ ሕግን ከሚቃወም ሥራ በቀር ሁሉንም ሊሠሩ ይገባል:: ... እንደ ዘፋኝነት; እንደ መጥፎ ጫወታ; በእግር እንደ ማሸብሸብ(ዳንስና ጭፈራ) ካልሆነ በቀር ነው::" (ፍት.ነገ.መን.አን. 23:820) ይህ የአበው ቃል ዘፋኝነት በመንፈሳዊ እይታ እንደ ሥራ መቆጠር እንደሌለበት ያስረዳል::
❖ ዘፋኝነት "የሥጋ ሥራ" በመሆኑ ኃጢአት ነው:: የሚዘፍን የእግዚአብሔርን መንግስት ሊያይ አይችልም። (ገላ.5:21):: "በመንፈስ ተመላለሱ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ;" ተብሏልና:: (ገላ.5:16)::
❖ ዘፈን በመንፈሳውያን መጻሕፍት ተወግዟል:: ሐዋርያት በዲድስቅልያ "ኢትኩኑ ዘፈንያነ" ; "ዘፋኞች አትሁኑ" ብለዋል:: (ዲድስ.አንቀጽ 7) ቅዱስ ጳውሎስ "በቀን እንደምንሆን በአግባብ እንመላለስ:: በዘፈንና በስካር አይሁን" ብሏል:: (ሮሜ.13:13) ቅዱስ ጴጥሮስ ደግሞ "በስካርና በዘፈን የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል::" ይለናል:: (1ኛ.ጴጥ.4:3):: መጽሐፈ ሐዊ ደግሞ "ከሰይጣን የተገኘ ነውና ዘፈንንና ዳንስን ከኛ ማራቅ ይገባናል::" ይለናል:: (መጽ.ሐዊ አን. 50):: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ደግሞ ከማዘዝ አልፎ ዘፈንን እንተው ዘንድ "ዘፈንን ትተዉ ዘንድ እማልዳችሗለሁ;" በማለት ይማጸናል:: (ተግ.ዘዮሐ.አፈ.28) ዘፈንን አንተውም ላሉ ደግሞ መጽሐፈ ሐዊ "በዘፈን ጸንተው የሚኖሩ ይፈረድባቸዋል" በማለት ሲያስጠነቅቅ እናገኛለን:: (መጽ.ሐዊ.አን. 12)::
❖ ሁላችሁ ወዳጆቼ የእኛ ሳይሆን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሆነውን ሰውነታችንን በከንቱ ዘፈን ዳንኪራ እና ጭፈራ አናርክሰው። እግዚአብሔር በባህርይው ንፁህ ይወዳልና ሰውነታችንን አንፅተን እንደተዘጋጀን የእርሱ ማደሪያ እና መቀደሻ እንድንሆን ፈቃዱ ይሁንልን።
ለ) መጽሐፍ ለምን በዘፈን አመስግኑ ይላል።
==============================
በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስትምህሮ መሰረት ዘፈን መስማት ፣ መዝፈንም ሆነ በዘፈኑ መጨፈር የተከለከለ ነው ።ይህም የሆነው በሐዋርያት እና በሊቃውንት እንዳስተማሩን በእግዚአብሔር የተወገዘ ስለሆነ ነው። በቤተክርስትያናችን ዘፈን የማይፈቀድባቸውን ምክንያቶች መጽሐፍ በዘፈን የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃል ። 1ኛ ጴጥ 4፤3 እንዲሁም ዘፈን የሥጋ ሥራና የዝሙት ማቀንቀኛ ስለሆነ ነው።( ማቴ14፤ 4 ገላ 5 ፣19 )ጥቂቶች ታዲያ የፅሁፉን መሰረታዊ ሀሳብ በጥልቀት ባለመረዳት እና ከመፅሐፍ ቅዱስ ላይም አገናዝበው ባለማስተዋል ተወዛግበውበታል። በተለይ በመፅሐፍ ቅዱስ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ "እግዚአብሔርን በዘፈን አመስግኑ" የሚል ስለተፃፈ.. . አሁን በየምሽት መዝናኛዎች (Night clubs) የምንሰማውን ዘፈን መልካም እንደሆነ በማሰብ በሌላም በኩል መፅሐፍ ቅዱስ ዘፈንን እንደሚደግፍ አድርገው ማስረጃ ሳይቀር እየጠቀሱ ሲከራከሩ እንሰማንለ። ዛሬ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በመፅሐፍ ቅዱስ ዘፈን የሚለውን እንነጋገራለን። የቤተክርስትያናችን ሊቃውንት እንደሚያስተምሩት ድሮ በኖኅ ዘመን የሰው ዘር ከኖኅ ቤተሰቦች በስተቀር በእግዚአብሔርቀር በንፍር ውሃ እንዲጠፉ ካደረግው ምክንያት አንዱ ዘፈን ነው። ይሄውም በደብር ቅድስት የነበሩት የሴት ልጆች በቃየን ዘመዶች ዘፈን ተማርከው ለዝሙት በመጋለጣቸው ረክሰው እግዚአብሔርም ሰውን በመፍጠሩ እስከ መፀፀት እንደደረሰ ያስተምራሉ። እግዚአብሔር ተፀፀተ ስንል እርሱ በባህርይው በሚያደርገው ነገር የሚቆጭ ሆኖ ሳይሆን የሰው ልጅ ክፋት የቱን ያህል እንደሆነ ለማስረዳት ነው። ዘፈን ወደ ኃጢአት የሚመራ የአጋንንት ስራ ነው። በዚህም ምክንያት በቅድስት ቤተክርስትያናችን ፈፅሞ የማይፈቀድ የረከሰ ተግባር ነው። ሐዋርያት በመፅሐፈ ዲድስቅልያ ላይ እንዲህ ብለው ደንግገዋል " ዘፋኞች አትሁኑ" ብለዋል። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም "ከማዘንም አልፎ ዘፈንን ትተው ዘንድ እንማልዳችኋለን" በማለት በመፅሐፉ ላይ ያሳስባል። የኃጢአት ጥሩ ባይኖርም የዘፈን ሀጢአትነት ግን የከፋ ነው ። ይህም የሆነበት ሰዎችን በማታለል እና በመገፋፋት ለተለያዩ መዳራት ፣ ዝሙት እና ርኩሰት ስለሚገፋፈ ነው። በተለይ እኛ ወጣቶች ለሁሉ ነገር ችኩል እና ስሜታዊ በመሆናችን ጠላታችን ዲያቢሎስ የእርሱ መለያ ብቻ በሆነው በዘፈኑ እያታለለ ወደእግሩ ሲጥለን ይታያል። ኃጢአት ወደእኛ እንዲቀርብ እንደ ምክንያት ሆኖ ከፍተኛውን አስተዋፅኦ የሚያበረክተው ይሄው ዘፈን ነው። ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ ስለሚከለክሉን ከዘፈን ልንርቅ ይገባናል ማለት ነው።
❖ መዝሙር ዘፈን ሊባል ይችላልን?? በመፅሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን በዘፈን አመስግኑ ለምን ተባለ??
መዝሙር እና ዘፈን የሚሉት ቃላት በመፅሐፍ ቅዱሳችን በአንዳንድ ቦታዎች ላይ አንድ የሚያደርጋቸው ነገር አለ። ይሄውም ሁለቱም ቃላት "ኅለየ " ሃሌ ሃሌ ከሚለው የግእዝ ግስ ትርጓሜ የወጡ ሰለሆነ ነው። የቤተ ክርስትያናችን የቀድሞ ሊቃውንት "ኅለየ" የሚለውን በአንድ በኩል "ዘመረ ፤ አመሰገነ" ብለው ሲተረጉሙት በሌላም በኩል "ዘፈነ" ይላል ብለው ያስተምራሉ። በተጨማሪም ሁለቱም ዜማ ያላቸው በመሆኑ ሊመሳሰሉ ይችላል። ከላይ እንደነገርኳችሁ ዘፈን እና መዝሙር የሚሉት በመጽሐፋችን ተለዋዋጭነት ስላላቸው በተለያዩ ቦታዎች ላይ በዘፈን አመስግኑ ተብሏል።ሁለቱ ቃላት የትርጉም ተወራራሽነት እንዳላቸው ምሳሌ እንስጣችሁ።
" ስሙን በዘፈን ያመስግኑ ፤በከበሮና በመሰንቆም ይዘምሩለት " (መዝሙር 149:3) ። በዚህ የእግዚአብሔር ቃል ላይ ያሉት ሁለቱ አረፍተ ነገሮች መልእክት በተመሳሳይ እግዚአብሔር የሚቀበለውን ስለማድረግ ነው። "በዘፈን" የተባለው ስጋን ስለሚያስደስተው ሳይሆን በረከት ስለሚገኝበት መዝሙር መሆኑን ልናውቅ ይገባናል። "ይዝፈኑለት" እና "ይዘምሩለት" የሚሉት ቃላት የትርጉም ተወራራሽነት ባይኖራቸው ኖሮ በዚህ አግባብ መፅሀፍ ቅዱስን የሚጋጭ ልንለው ባልን ነበር። ከላይ "ስሙን በዘፈን ያመስግኑ" ብሎ ያስቀመጠው አሁን እኛ በስጋና ደም በምናውቀው ወደ ስካር እና ዝሙት ስለሚስበው "አስረሽ ምችው " ሳይሆን እግዚአብሔር የሚቀበለው እና በረከት የሚገኝበት መንፈሳዊ መዝሙር ነው። "የእግዚአብሔር ታቦት ወደ ዳዊት ከተማ በገባ ጊዜ የሳኦል ልጅ ሜልኮል በመስኮት ተመለከተች ። ንጉሱም ዳዊት በእግዚአብሔር ፊት ሲዘፍን ተመልክታ በልብዋ ናቀችው። እግዚአብሔርም ሜልኮልን እስክትወልድ ልጅ አልሰጣትም። (መ.ሳ.ቀ 6:16-23) በዚህም የመፅሀፍ ቅዱስ ክፍል ዘፈን የተባለው እግዚአብሔር የሚቀበለው እና የሚመለክበት ባይሆን ኖሮ ዳዊትን በዘፈኑ ያቃለለችው ሜልኮል ልጅ እንዳትወልድ ባልሆነች ነበር። የቤተክርስትያን አባቶቻችን ይሄንን ትክክል ያልሆነ ትርጓሜ በመረዳት በ2ሺህ ዓ.ም በብፁእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የፓትርያርክነት ዘመን ከግሪኩ፣ ዕብራዊው ፤ግእዙ እና ከሰባው ሊቃናት መፅሐፍት በማመሳከር በታተመው መፅሐፍ ቅዱሳችን ተስተካክሎ ይገኛል። በመዝ149: 3 እና በሌላም ክፍል ላይ "በዘፈን" የሚለውን " በሽብሸባ" ተብሎ ተስተካክሏ
Негізгі бет ዘፈን እና መዝሙር
Пікірлер: 93