ዛጎል የመጻሕፍት ባንክ በሀገራችን የመጀመሪው የመጻሕፍት ባንክ ሲሆን የተመሠረተው በ2013 ዓ.ም. ነው፡፡ የባንኩ መስራች የ13 መጻሕፍት ደራሲ የሆነው እንዳለጌታ ከበደ ነው፡፡
ደራሲ እንዳለ ጌታ ከበደ በኢትዮጵያ ሣይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የሥነጥበባት ማዕከል ዳይሬክተር ሆኖ ሰርቷል፡፡
የመጀመሪያው የበጎ ሰው ሽልማት ተሸላሚ የነበረው ደራሲ እንዳለጌታ የጀመረው ዛጎል የመጻሕፍት ባንክ የመጻሕፍት እጥረት ላሉባቸው ትምህርት ቤቶች፣ ማረሚያ ቤቶች፣ የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት፣ በግላቸው ቤተ መጻሕፍት ላላቸውና ሌሎችም የሰበሰባቸውን መጻሕፍት በነጻ ይለግሳል፡፡
በተጨማሪም ባንኩ በየሳምንቱ ቅዳሜ ጠዋት ከ 4:00-6:00 ድረስ አንድ ደራሲ አዲስ ያወጣውን መጽሐፍ ይዞ ከአንባቢዎቹ ጋር የሚተዋወቅበትን ፕሮግራም እያካሄደ ይገኛል፡፡
Негізгі бет ዛጎል - በሀገራችን የመጀመሪያው የመጻሕፍት ባንክ
No video
Пікірлер: 19