የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በነገው ዕለት ለሚያካሄደው ጠቅላላ ጉባኤም ሆነ በጉባኤው ላይ ለሚተላለፉ ውሳኔዎች በሙሉ “እውቅና እንደማይሰጥ” አስታወቀ። ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ከማድረጉ 21 ቀናት በፊት ለምርጫ ቦርድ ማሳወቅ እና ፓርቲው በሚያደርገው ጠቅላላ ጉባኤ የቦርዱ ታዛቢዎች መገኘት እንደነበረባቸውም አስታውቋል።
ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ይህን ያስታወቀው፤ ዛሬ ሰኞ ነሐሴ 6፤ 2016 ለህወሓት በጻፈው ደብዳቤ ነው። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ፊርማ ያረፈበት ይህ ደብዳቤ፤ ህወሓት “ጠርቶታል” የተባለውን ጠቅላላ ጉባኤ የሚመለከት እንደሆነ በመግቢያው ላይ ተቀምጧል።
ይኸው ደብዳቤ፤ ህወሓት በቦርዱ “በልዩ ሁኔታ” እንዲመዘገብ ከተደረገ በኋላ ከቦርዱ የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንደተሰጠው አስታውሷል። ህወሓት ይህ የምስክር ወረቀት ከደረሰው በኋላ የሚተዳደረው፤ በ2011 ዓ.ም በወጣው እና ባለፈው ግንቦት ወር በተሻሻለው፤ የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ መሰረት መሆኑንም ቦርዱ ጠቅሷል።
ቦርዱ ይህን አዋጅ መሰረት በማድረግ ባለፈው ሳምንት አርብ ካሳለፋቸው ውሳኔዎች መካከል፤ የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ የሚመለከተው እንደሚገኝበት በዛሬው ደብዳቤው አመልክቷል። ቦርዱ በዚሁ ውሳኔው፤ ህወሓት በልዩ ሁኔታ ከተመዘገበበት ዕለት ጀምሮ ባሉት ስድስት ወራቶች ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ማድረግ እንዳለበት አሳስቦ ነበር።
ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ከማድረጉ ከ21 ቀናት በፊት ለምርጫ ቦርዱ ማሳወቅ እንዳለበትም በውሳኔው ላይ ሰፍሯል። ቦርዱ ይህን ቀነ ገደብ የሰጠው “የፓርቲውን የቅድመ ጉባኤ ዝግጅት የተመለከቱ ስራዎችን ለመከታተል እንዲረዳው” መሆኑን በወቅቱ ገልጿል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
ተጨማሪውን ለማንበብ ይሄን ሊንክ ይጫኑ ethiopiainside...
-------------------------------------------------------------------------------------------
የ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ትኩስ ዜናዎችን እና ወቅታዊ ዘገባዎችን ለመከታተል፦
ድረ ገጽ ፦ ethiopiainsider...
ፌስቡክ ፦ / ethiopiainsider
ትዊተር (ኤክስ) ፦ / ethiopiainsider
ቴሌግራም፦ t.me/EthiopiaI...
ቲክቶክ፦ / ethiopiainsider
Негізгі бет ዛሬ ነሐሴ 7 ለሚካሄደው የህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ፤ ምርጫ ቦርድ “እውቅና አልሰጥም” አለ
Пікірлер