አርዕስተ ዜና
*ወደ ሶማሊያ እየገባ ነው በተባለ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ጉዳይ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ እየተካሰሱ ነው ። የሁለቱም ሃገራት ውጭ ጉዳይ ሚንሥትሮች አንዱ የሌላኛውን ሀገር በህገወጥ የጦር መሣሪያ ማቀበል ጉዳይ ከስሷል ።
*በመከላከያ ሠራዊት እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከአንድ ዓመት በላይ ውጊያው በቀጠለበት የአማራ ክልል ባለፈው ዓመት መማር ከነበረባቸው ተማሪዎች ግማሽ ያህሉ አለመማራቸው ተገለጠ ።
*እሥራኤል እና የሊባኖሱ ሒዝቦላህ ዛሬም በሮኬቶች እና በጦር ጄቶች ድብደባ ፈጸሙ ። እሥራኤል በድጋሚ የሊባኖስ ዋና ከተማ ቤሩትን ከአየር ላይ በቦንብ ከደበደበች በኋላ እስካሁን የሞቱት ሰዎች ቁጥር ወደ 560 መድረሱን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል ።
*የሩስያ ጦር እንደ ጎርጎሪዮስ አቆጣጠር በ2022 ጦርነቱን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ታይቶ በማይታወቅ ፍጥነት በምሥራቅ በኩል እመርታ ዕያሳየ መሆኑም ተዘግቧል ። ጦሩ ዶንባስ ግዛት ውስጥ እየገሰገሰ ነው ተብሏል ።
Негізгі бет DW Amharic የማክሰኞ መስከረም 14 ቀን፣ 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና
Пікірлер: 4