#ኤረርተራራ
#gizetube #ethiopian #ortodox
የኢትዮጵያን ትንሳኤ እየጠበቁ ያሉ ኤረር ተራራ የሰወራቸው አዳም ከገነት ያመጣቸው ስድስቱ የክብር ዕቃዎች በዚህ በኢትዮጵያ ስለ መኖራቸው ምን ያህሎቻችን እናውቅ ይሆን? የኢትዮጵያ ትንሣኤ አብሣሪ ንጉሥ ቴዎድሮሥ መነሻ ሥፍራ!
በአለማችን ላይ ድብቅና ሚሥጥራዊ ተብሎ ከሚነሡ ታላላቅ ሥፍራዎች አንዱ በቀዳሚነት ደረጃ ይዞ የሚገኘው የኢትዮጺያው ኤረር ተራራ ነው።ኤረር ብዞዎች የሚያውቁት የረር በሚለው ነው.... ይህ ተራራ ደግሞ የሚገኘው ከአዲስ አበባ በምስራቅ አቅጣጫ ላይ ነው፡፡ ፨እንደ መጽሐፈ ነገደ አዳም አገላለጽ በታላቁና በመጨረሻው ክብር ደረጃ ላይ ለምትገኘው ጥበብ ማዕከላዊ ስፍራ የሆነው ኤረር ነው ይለናል፡፡ ይህንን በኋላ ላይ በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ የተጻፈው ድርሳነ ኡራኤል ኤረር ተራራን የኢትዮጵያ ማዕከላዊ ቦታ ነው ይለዋል፡፡ መጽሐፈ ነገደ አዳም የኤረር ተራራ ስፋት ወይም ይህ ስፍራ የሚያካልላቸው ስፍራዎች በሰሜን እስከ እንጦጦ ተራራ፣ በምዕራብ እስከ ፉሪ ተራራ፣ በደቡብ እስከ ዝቋላ ተራራና በምስራቅ እስከ ቱሉ ፈራ ተራራ ድርስ እንደሆነ ይገልጻል፡፡ ፨ኤረር ማለት ከሰባቱ የሰማያተ ሰማያት ሥፍራዎች ውስጥ አንዱ የሆነው የቅዱሳን መላእክት ከተማ ስም ነው ፡፡ ይህም ተራራ የታላቋ ጥበብ መንፈስ ምንጭ ሥፍራ በመሆኑ በቅዱሳን መላእክቱ ከተማ ስም ኤረር ተብሎ ይጠራል፡፡ ውድ የግዜ ቲዩብ ቤተሰቦች በኤረር መላእክት ይዘንባሉ፣ የኢትዮጵያ ብዙ ቅዱሳን አባቶችም በዓታቸው አድርገውታል ይህንን ምስጢራዊ ኤረር ተራራ... ይህ አስደናቂ ተራራ የያዛቸው ምስጢሮች፣ ያቀፋቸው እውነቶች አይጠገቤ ናቸው፡፡
ሰላም ይኑረን ተስፋን አንጣ ውድ የግዜ ቲዩብ ቤተሰቦች እንደምን ሰነበታችሁ የእግዚአብሔር ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን በዛሬው መርሀግብራችን የረር ያቀፋቸውን አባታችን ቅዱስ አዳም ከገነት ይዟቸው የመጣቸውን 6ቱን የክብር እቃዎች እንመለከታለን.... ሰናይ ቆይታ ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ...ግዜ ቲዩብ!
Негізгі бет Ойын-сауық 🔴👉ኤረር ተራራ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እየጠበቁ ያሉ አዳም ከገነት ወደ ምድር ያመጣቸው ምስጢሮች
Пікірлер: 91